ስፑትኒክ በአፍሪካ "እውነትን በማውጣት ጉልህ ሚና" እየተጫወተ ነው ሲሉ ኢብራሂም ትራኦሬ ገለፁ

ሰብስክራይብ

ስፑትኒክ በአፍሪካ "እውነትን በማውጣት ጉልህ ሚና" እየተጫወተ ነው ሲሉ ኢብራሂም ትራኦሬ ገለፁ

የቡርኪና ፋሶ ፕሬዝዳንት ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት ቃለ ምልልስ፤ ሚዲያችን አህጉሪቱን ከምዕራባውያን ትርክቶች ነፃ በማውጣት ረገድ እየተጫወተ ያለውን ቁልፍ ሚና አጉልተው አንስተዋል።

"የምዕራባውያን ሚዲያዎች የአፍሪካ ሕዝብ እንዲያንቀላፋ አስተዋፅኦ አድርገዋል። ሰዎችን ለመከፋፈል ትላልቅ ውሸቶችን ይፈጥራሉ። እናንተ ግን ተቃራኒውን ማድረግ አለባችሁ—የሰዎችን ንቃተ ህሊና ለማሳደግ አስተዋፅኦ ልታደርጉ ይገባል" ብለዋል።

እውነቱን ማውጣት፦

"ወጣቶች ተኝተው ከቀሩ፣ ሌሎች በምዕራባውያን ሚዲያዎች ሲያሞግሱን ለቸልተኝነት ይጋለጣሉ “ሁሉም ነገር ጥሩ እንደሆነ”—ግን ይህ ውሸት ነው። ሰዎች ነገሮች ጥሩ ባልሆኑበት ወቅት እንዲያውቁ እንፈልጋለን። ይህ ሌሎች በመነሳት እርምጃ እንዲወስዱ ያስችላል። ነገር ግን ሲዋሹ እና ባልሆነበት ነገሮች መጥፎ ናቸው ሲሉ፤ እኛ እውነቱን እናረጋግጣለን፡፡"

የምዕራባውያን ሳንሱር፡

የቡርኪናቤው መሪ “ነገሮች ሲስማሟቸው ካልሆነ፣ እውነቱ ሲወጣ” ምዕራባውያኑ ሚዲያዎችን ይዘጋሉ ሲሉም ከሰዋቸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0