የኦሮሚያ ክልል የተፈጥሮ ሃብትን ወደ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመቀየር "ኦ-ማይኒንግ" የተሰኘ እቅድ በይፋ አስጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኦሮሚያ ክልል የተፈጥሮ ሃብትን ወደ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመቀየር "ኦ-ማይኒንግ" የተሰኘ እቅድ በይፋ አስጀመረ
የኦሮሚያ ክልል የተፈጥሮ ሃብትን ወደ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመቀየር ኦ-ማይኒንግ የተሰኘ እቅድ በይፋ አስጀመረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.05.2025
ሰብስክራይብ

የኦሮሚያ ክልል የተፈጥሮ ሃብትን ወደ ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እድገት ለመቀየር "ኦ-ማይኒንግ" የተሰኘ እቅድ በይፋ አስጀመረ

እቅዱ የግል ዘርፍ ኢንቨስትመንትን ማበረታታት፣ የማዕድን ሥራን ማስፋፋት እና የወጪ ንግድን ማሳደግ ላይ አነጣጥሯል።

የኦሮሚያ የማዕድን ልማት ባለሥልጣን በክልሉ ከፍተኛ የወርቅ፣ የከበሩ ድንጋዮች እና የኢንዱስትሪ ማዕድናት ክምችት እንደሚገኝ የዳሰሳ ጥናቶች ያመለክታሉ ብሏል።

ክልሉ ማዕድናቱን ማውጣት ብቻ ሳይሆን በሀብቶቹ ዙሪያ የዳበረ የኢንዱስትሪ ምህዳር ለመመሥረት አስቧል።

በተጨማሪም ከወጪ ንግድ እና እሴት በሚጨምሩ ኢንዱስትሪዎች የዘርፉን ገቢ በሦስት እጥፍ ለማሳደግ እና የክልሉን ኢኮኖሚ ለመለወጥ መወጠኑን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0