ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ የ2025 ዲጂታል እቅድን ሙሉ በሙሉ አሳክታለች አሉ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ የ2025 ዲጂታል እቅድን ሙሉ በሙሉ አሳክታለች አሉ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ የ2025 ዲጂታል እቅድን ሙሉ በሙሉ አሳክታለች አሉ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.05.2025
ሰብስክራይብ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያ የ2025 ዲጂታል እቅድን ሙሉ በሙሉ አሳክታለች አሉ

“አሁን ዲጂታል 2030 እቅድ እየተዘጋጀ ይገኛል። ይህ እውን የሚሆን ከሆነ በሀገራችን እውቀት መር ኢኮኖሚ ለመገንባት መሠረት ይጥላል” ሲሉ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ በሰጡት ቃል ምልልስ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በሁሉም ዘርፎች ቴክኖሎጂን የመጠቀም ልምምድ እያደገ መምጣቱንም ገልጸዋል። ለአብነትም በሲቪል ሰርቪስ፣ በሕግ ማስከበር፣ በመከላከያ፣ በሚዲያ፣ በግብርና እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ያሉ ሥራዎችን ለማሳካት እና ለማሳለጥ ጥቅም ላይ እዋለ እንደሆነ አንስተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ“ቻት ጂፒቲ” ወይም “ዲፕ ሲክ” ጋር ተመሳሳይ የሆነ “መላ” የተሰኘ የሀገር ውስጥ ቋንቋን በስፋት የሚጠቀም የሰው ሰራሽ አስተውሎት ሥርዓት መገንባቱንም አስታውቀዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0