"ሩሲያ በአሁኑ ጊዜ በተሻለ ጂኦፖለቲካዊ አቋም ላይ ትገኛለች" ሲሉ ሜክሲካውያን የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ"ሩሲያ በአሁኑ ጊዜ በተሻለ ጂኦፖለቲካዊ አቋም ላይ ትገኛለች" ሲሉ ሜክሲካውያን የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ተናገሩ
ሩሲያ በአሁኑ ጊዜ በተሻለ ጂኦፖለቲካዊ አቋም ላይ ትገኛለች ሲሉ ሜክሲካውያን የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 11.05.2025
ሰብስክራይብ

"ሩሲያ በአሁኑ ጊዜ በተሻለ ጂኦፖለቲካዊ አቋም ላይ ትገኛለች" ሲሉ ሜክሲካውያን የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ተናገሩ

የሜክሲኮ የራስ አገዝ ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ ምሁር ካርሎስ ማኑዌል ሎፔዝ አልቫራዶ ለስፑትኒክ በሰጡት ቃል "ቭላድሚር ፑቲን በድርድሩ የበለጠ ኃይል ይኖራቸዋል" ብለዋል።

እንደ ባለሙያው ገለጻ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ከግዛት ጉዳዮች እና ከኪዬቭ ኔቶን አለመቀላቀል ጋር የማይጣረሱ ጉዳዮችን በተመለከት የዩክሬን ጥያቄዎችን ሊቀበሉ እንደሚችሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።

የፑቲን የሰላም ሃሳብ የተለያዩ ሀገራትን እና መሪዎችን አንድ አድርጎ እና የዓለምን ባለብዙ ዋልታነት አሳይቶ በስኬት ከተጠናቀቀው የድል ቀን በኋላ የመጣ ነው ብለዋል።

አልቫራዶ ድርድሩ ለዘላቂ የሰላም አፈታት ሂደት መደላደል እንደሚፈጥር እና በዓመቱ መጨረሻ ስምምነት ላይ ሊደረስ እንደሚችል ገልጸዋል።

ሌላኛው የዩኒቨርስቲው ባለሙያ ዳንኤል ጋራይ ሳልዳና ሩሲያ በአሁኑ ጊዜ ምቹ በሆነ የጂኦፖለቲካዊ አቋም ላይ እንደምትገኝ ተናግረዋል።

"በመጀመሪያ ደረጃ ፑቲን የራሳቸውን አቋም የሚገልፁ ሃሳቦችን የማቅረብ አቅማቸው ላይ እርግጠኛ ናቸው" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0