ፑቲን በኢስታንቡል ቀጥተኛ የሰላም ንግግር ለመጀመር ባቀረቡት ጥሪ ዙሪያ የተሰጡ አስተያየቶች፦
11:11 11.05.2025 (የተሻሻለ: 11:34 11.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱፑቲን በኢስታንቡል ቀጥተኛ የሰላም ንግግር ለመጀመር ባቀረቡት ጥሪ ዙሪያ የተሰጡ አስተያየቶች፦

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፑቲን በኢስታንቡል ቀጥተኛ የሰላም ንግግር ለመጀመር ባቀረቡት ጥሪ ዙሪያ የተሰጡ አስተያየቶች፦
የሩሲያ ምክር ቤት አባል አንድሬ ክሊሻስ
"የዘለንስኪ 'ወዳጆች' የተቻላቸውን ሁሉ ቢያደርጉም፤ የዩክሬን ተነሳሽነት በወታደራዊም ሆነ በዲፕሎማሲያዊ ሙሉ በሙሉ የሩሲያ ነው።"
የሩሲያ የምክር ቤት አባል ኮንስታንቲን ኮሳቼቭ
"ሁለት አማራጮች። የሰላም ተስፋ የሌለበት ያለ ድርድር የሚደረግ የተኩስ አቁም ወይም ወደ ሰላም የሚያመራ ድርድር። የመጀመሪያው ሃሳብ የኪዬቭ ባለሥልጣናት ነው። ይህም በ30 ቀን ውስጥ ወታደራዊ ኃይልን መልሶ በማደራጀት ጦርነቱን መቀጠል ማለት ነው። ሁለተኛው 'ለሰላም ዕድል መስጠት' ነው።"
የቱርክ የታሪክ ምሁር መህመት ፔሪንሴክ
"ኪዬቭ ወይ ወደ ድርድር ጠረጴዛው ትመጣለች አልያም አሻፈረኝ በማለት የአንካራን ሽምግልና ታጣለች።"
የቦሊቪያ ፓርላማ አባል ሄርገስ ሜርካዶ
"የፑቲን የሰላም ተነሳሽነት በጣም አስደሳች ነው፤ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ቢስማሙበት ይመረጣል እንዲሁም ለዓለም ሰላም ሲባል ያለ አሸማጋዮች ቀጥተኛ ውይይት ቢደረግ የተሻለ ነው።"
የቦሊቪያ የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፈርናንዶ ሁዋናኩኒ
"ይህ ሩሲያ ለሰላም ቁርጠኛ መሆኗን ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ በግልጽ የሚያመለክት ነው...ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ዩክሬን በዚህ ድርድር ላይ እንድትሳተፍ በማድረግ ትልቅ ሚና መጫወት አለበት።"
አርጀንቲናዊው የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ ማርሴሎ ሞንቴስ
"የሩሲያ እና የዩክሬን አቋሞች አሁንም ጠንከር ያሉ ናቸው፤ አውሮፓ ለዘለንስኪ የምታደርገው ድጋፍ የሰላም ስምምነት ላይ እንዳይደረስ መዘግየትና መወሳሰብ ፈጥሯል።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X