የፑቲን እና ትራኦሬ የዛሬ ምሽት ውይይት "መከላከያ፣ ትምህርት እና የባለብዙ ዋልታ ዓለም" ላይ እንደሚያተኩር የቡርኪናፋሶው መሪ ገለፁ
17:28 10.05.2025 (የተሻሻለ: 17:44 10.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየፑቲን እና ትራኦሬ የዛሬ ምሽት ውይይት "መከላከያ፣ ትምህርት እና የባለብዙ ዋልታ ዓለም" ላይ እንደሚያተኩር የቡርኪናፋሶው መሪ ገለፁ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የፑቲን እና ትራኦሬ የዛሬ ምሽት ውይይት "መከላከያ፣ ትምህርት እና የባለብዙ ዋልታ ዓለም" ላይ እንደሚያተኩር የቡርኪናፋሶው መሪ ገለፁ
የቡርኪናፋሶው ፕሬዝዳንት ዛሬ ከሩሲያው አቻቸው ጋር ከሚያደርጉት ስብሰባ በፊት ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት ሩሲያ እና ቡርኪናፋሶ "ተመሳሳይ አመለካከት" አላቸው።
ኢብራሂም ትራኦሬ "ነጻ፣ ባለ ብዙ ዋልታ፣ ሰዎች ነጻ፣ ሉዓላዊ እና የፈለጉትን የሚሆኑበት ዓለም በመፍጠር ረገድ ተመሳሳይ አመለካከት አለን" ብለዋል።
ሁለቱ መሪዎች የቡርኪናፋሶ ወጣቶችን ማሰልጠን ጨምሮ በትምህርት ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ።
ኢብራሂም ትራኦሬ ሲያብራሩ "ብዙ ጎበዝ እና ብልህ፣ በሳይንስ ጥሩ የሆኑ ቡርኪናፋሶያውያንን ማሰልጠን ያስፈልጋል። ሀገሪቱን ማሳድግ የሚቻለው በሳይንስ ነው" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X