የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት የድል ቀንን አስመልክቶ ለፑቲን የመልካም ምኞታቸውን ገለፁ
17:25 09.05.2025 (የተሻሻለ: 17:44 09.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት የድል ቀንን አስመልክቶ ለፑቲን የመልካም ምኞታቸውን ገለፁ
"የድል ቀን - የሩሲያ ሕዝብ ለነፃነት እና ለሰላም ባደረገው ትግል ያሳየውን ጀግንነት፣ ጽናት እና መስዋዕትነት የሚያመለክት ታላቅ ቀን ነው" ሲሉ ሳሚያ ሱሉሁ በኤክስ ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
በታላቁ የአርበኝነት ጦርነት 80ኛ ዓመት ክብረ በዓል በከባድ ትግል የተገኘ ድል የሚታውስበትና ለሩሲያ ሕዝብ ጀግንነትና ጽናት ማረጋገጫ ነው ሲሉ የታንዛኒያ ፕሬዝዳንት ገልጸዋል።
"ዛሬም እንዳለፈው የዚህ አስደናቂ ቀን ትውስታ ሁሉም ሀገራት ለሰላም፣ ለፍትሕ እና ትብብር እንዲቆሙ ያነሳሳቸዋል" ብለዋል።
ሱሉሁ አክለውም ታንዛኒያ ከሩሲያ ጋር ላላት "ጠንካራ ወዳጅነት" ትልቅ ቦታ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X