ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በማዕድን ዘርፍ የሚያደርጉት ትብብር ሁለቱንም ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ባለሙያዎች ተናገሩ
20:42 08.05.2025 (የተሻሻለ: 21:04 08.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ እና ሩሲያ በማዕድን ዘርፍ የሚያደርጉት ትብብር ሁለቱንም ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ባለሙያዎች ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በማዕድን ዘርፍ የሚያደርጉት ትብብር ሁለቱንም ሀገራት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ባለሙያዎች ተናገሩ
በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ የጂኦሳይንስ ክፍል ረዳት ፕሮፌሰር በቀለ አየለ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቃለ-ምልልስ በኢትዮጵያ የማዕድን ፍለጋ ታሪክ ውስጥ የሩሲያውያን ጂኦሎጂስቶች ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።
"ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር አብራ በመሥራቷ ትጠቀማለች። እኔ እንደማስበው ኢትዮጵያ ከሩሲያ የላቁ ቴክኖሎጂዎችን ማግኘት ትችላለች" ሲሉ ተናግረዋል።
የማዕድን አማካሪው ሙስጠፋ ሻይቶ በበኩላቸው ስለ ኢትዮጵያ የማዕድን ፍለጋ እና ልማት ሲነሳ የሩሲያን አስተዋፅኦ መርሳት አይቻልም ብለዋል።
"ሩሲያውያን ኢትዮጵያ ምን እንዳላት እና የሥነ-ምድር አመሠራረቷን ያውቃሉ። ሀለቱ ሀገራት በማዕድን ዘርፍ የሚያደርጉት ትብብር አሁን ያለንን እና ወደፊት ሊገኙ የሚችሉ ማዕድናትን እንድናውቅ ያስችላል" ሲሉ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X