ማዳጋስካር የሁለተኛው ዓለም ጦርነት የሶቭየት ወታደሮችን ጀግንነት አወደሰች
15:10 08.05.2025 (የተሻሻለ: 15:44 08.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ማዳጋስካር የሁለተኛው ዓለም ጦርነት የሶቭየት ወታደሮችን ጀግንነት አወደሰች
በዋና ከተማዋ አንታናናሪቮ በትላንትናው ዕለት በተደረገው ዝግጅት ናዚ ጀርመን ድል የተደረገበት 80ኛ ዓመት መታሰቢያ በዓል ተከብሯል።
በበዓሉ ላይ ግንባር ቀደም ፖለቲከኞች እና የዲፕሎማቲክ ማሕበረሰቡን ጨምሮ ከ400 በላይ ታዳሚዎች ተሳትፈውበታል።
"የሩሲያ ወዳጆች በማዳጋስካር" የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ባዘጋጀው የመታሰቢያ ቀን መርሐ-ግብር፦
⏺ የሙዚቃ ድግስ
⏺ ዘጋቢ ፊልም እና
⏺ የሩሲያ-ማላጋሲ ግንኙነቶችን የሚያሳይ አውደ ርእይ ተካሂዷል።
የኅብረቱ ፕሬዝዳንት ሪቻርድ ራኮቶኒሪን ከ27 ሚልዮን በላይ ሰዎች ሕይወት በቀጠፈው ጦርነት የሶቪየት ኅብረት የተጫወተችውን ቁልፍ ሚና አብራርተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X