የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን በራስ ለመማር የሚያስችል መፅሐፍ ተመረቀ
11:48 07.05.2025 (የተሻሻለ: 14:54 07.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን በራስ ለመማር የሚያስችል መፅሐፍ ተመረቀ
መማሪያው የዲጂታል መተግበሪያ የተዘጋጀለት የቋንቋ ፎኖተ ካርታ እንደሆነ ተገልጿል፡፡
መፅሐፉ በ2012 ዓ.ም በፀደቀው የቋንቋ ፖሊሲ መሠረት በአምስቱ የፌዴራል ቋንቋዎች ማለትም፦
በአማርኛ፣
አፋን ኦሮሞ፣
በሶማሌ፣
በአፋርኛ እና
በትግረኛ የተዘጋጀ ነው፡፡
ፍኖተ ካርታው በኢትዮጵያ ብዝሃ ቋንቋን እና ህብረ ብሔራዊነትን ለማሳደግና ለማስተዋወቅ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል መባሉን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X