ሞስኮ በድል ቀን ወታደራዊ ሰልፍ ላይ 29 የውጭ መሪዎችን ትጠብቃለች
18:39 06.05.2025 (የተሻሻለ: 18:54 06.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሞስኮ በድል ቀን ወታደራዊ ሰልፍ ላይ 29 የውጭ መሪዎችን ትጠብቃለች
የፕሬዝዳንት ፑቲን ረዳት የሚከተሉትን ይፋ አድርገዋል፦
የብራዚል፣ የቻይና፣ የፍልስጤም እና የግብፅ መሪዎች በሞስኮ ወታደራዊ ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
የቬንዙዌላ በመሪ ደረጃ ትወከላለች፤ ፕሬዝዳንት ማዱሮ ከሚያዚያ 29 እስከ ግንቦት 1 ሩሲያን ይጎበኛሉ።
ህንድ፣ ኒካራጓ እና ደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ ልዑካኖቻቸውን ይልካሉ።
ሰሜን ኮሪያ በአምባሳደር ደረጃ ትሳተፋለች።
ከ13 ሀገራት የተውጣጡ የወታደራዊ ሰልፍ አቅራቢዎች በቀዩ አደባባይ ላይ በሚደረገው የግንቦት 1 ወታደራዊ ትርዒት ላይ ይሳተፋሉ።
ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ ከበርካታ የውጭ ሀገራት የተውጣጡ የቀድሞ ወታደሮች በሞስኮ የድል ቀን ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X