ፕሬዝዳንት ፑቲን በድል በዓል ወቅት ከ15 በላይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያካሂዳሉ ሲሉ የፕሬዝዳንቱ ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ አስታወቁ
17:37 06.05.2025 (የተሻሻለ: 17:54 06.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱፕሬዝዳንት ፑቲን በድል በዓል ወቅት ከ15 በላይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያካሂዳሉ ሲሉ የፕሬዝዳንቱ ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ አስታወቁ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፕሬዝዳንት ፑቲን በድል በዓል ወቅት ከ15 በላይ የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያካሂዳሉ ሲሉ የፕሬዝዳንቱ ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ አስታወቁ
⦁ ሚያዚያ 29 የሩሲያ ፕሬዝዳንት እና የቬንዙዌላ አቻቸው ኒኮላስ ማዱሮ የስትራቴጂክ አጋርነት እና ትብብር ስምምነት ይፈርማሉ፡፡
⦁ በተመሳሳይ ዕለት ፑቲን ከኩባ፣ ከሞንጎሊያ እና ከኮንጎ ፕሬዝዳንቶች ጋር ውይይት ያደርጋሉ፡፡
⦁ ሚያዝያ 30 ቀን የሀገሪቱ መሪ ከቻይናው ሺ ሺፒንግ ጋር ውይይት ያደርጋሉ፤ መሪዎች ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር የጋራ መግለጫዎችን ይፈራረማሉ፡፡
⦁ ግንቦት 1 ፑቲን እና የብራዚል አቻቸው በዩክሬን ያለውን ሁኔታ ይወያያሉ፡፡ በተጨማሪም የሩሲያው መሪ ከግብፅ ፕሬዝዳንት ጋር ይገናኛሉ፡፡
⦁ በተመሳሳይ ቀን ፑቲን ከሰርቢያ ፕሬዝዳንት እና ከስሎቫኪያ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሁም ከኡዝቤኪስታን ፕሬዝዳንት ጋር ይገናኛሉ፡፡
⦁ በግንቦት 2 ፑቲን ከቬትናም የኮሚኒስት ፓርቲ መሪ ጋር ውይይት ያደርጋሉ፡፡ በተጨማሪም የቡርኪናፋሶ እና የዚምባብዌ መሪዎችን ጨምሮ አምስት የሁለትዮሽ ውይይቶችን ያካሂዳሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X