የኢትዮጵያ የፊልም ሥራዎች በዓለም አቀፉ የዩሬዥያ ፊልም ፌስቲቫል ላይ የሚቀርቡበትን መንገድ በተመለከተ ውይይት ተካሄደ
12:49 06.05.2025 (የተሻሻለ: 13:34 06.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የፊልም ሥራዎች በዓለም አቀፉ የዩሬዥያ ፊልም ፌስቲቫል ላይ የሚቀርቡበትን መንገድ በተመለከተ ውይይት ተካሄደ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የፊልም ሥራዎች በዓለም አቀፉ የዩሬዥያ ፊልም ፌስቲቫል ላይ የሚቀርቡበትን መንገድ በተመለከተ ውይይት ተካሄደ
የኢትዮጵያ እና የሩሲያ የፊልም ባለሙያዎች በጉዳዩ ዙሪያ በፑሽኪን የባህል ማዕከል ምክክር አድርገዋል።
ታዋቂው የሩሲያ ፊልም ፕሮዲዩሰር እና የፑሽኪን ማዕከል ዳይሬክተር ሰርጌ ኖቮዚሎቭ በጉዳይ ዙሪያ ከኢትዮጵያ የፊልም እና የባህል ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።
ሀገራቱ በፊልም እና ባህል ያላቸውን አጋርነት ማጠናከር ያለመ እንዲሁም የጋራ የፊልም ፕሮጀክቶችን እና ለተማሪዎች የሚሰጡ ፕሮግራሞችን ያካተተ እንደነበር ከማዕከሉ የተገኘው መረጃ አመልክቷል።
የኢትዮጵያ ፊልሞች በ "ዩሬዥያ" የፊልም ፌስቲቫል ላይ መቅረባቸው የሀገሪቱን የፊልም ኢንዱስትሪ ለዓለም ለማስተዋውቅ እንደሚረዳ በውይይቱ ላይ መነሣቱ ተነግሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X