የኢትዮጵያ አየር መንገድ የናይጄሪያን የቱሪዝም ኢንደስትሪ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ
12:40 05.05.2025 (የተሻሻለ: 13:04 05.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ አየር መንገድ የናይጄሪያን የቱሪዝም ኢንደስትሪ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የናይጄሪያን የቱሪዝም ኢንደስትሪ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ
የአየር መንገዱ የናይጄሪያ ክልል ሥራ አስኪያጅ ፍሬህይወት መኮንን እንደገለፁት አየር መንገዱ ወደ ናይጄሪያ እና ከናይጄሪያ ወደ ሌሎች ሀገራት የሚደረገውን ቱሪዝም የማስተዋወቅ ጥረቱን ያጠናክራል ብለዋል።
"የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ንግድ እና ቱሪዝም አገናኝ ነው። ከዓለም ዙሪያ ወደ ናይጄሪያ ተጨማሪ ቱሪዝም ለመሳብ እንዲሁም ናይጄሪያውያን ኢትዮጵያን እና ሌሎች የአፍሪካ ክፍሎችን እንዲጎበኙ ለማበረታታት ቁርጠኛ ነን" ብለዋል ሲል የናይጄሪያ ሚዲያ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካላባር ካርኒቫልን ጨምሮ ዋና ዋና የናይጄሪያ ባህላዊ ዝግጅቶችን በተከታታይ በመደገፍ የቅናሽ ዋጋዎችን እና እንከን የለሽ የጉዞ አማራጮችን አቅርቧል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X