የኢትዮጵያ አየር መንገድ የናይጄሪያን የቱሪዝም ኢንደስትሪ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ
12:40 05.05.2025 (የተሻሻለ: 13:04 05.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የናይጄሪያን የቱሪዝም ኢንደስትሪ በማሳደግ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ
የአየር መንገዱ የናይጄሪያ ክልል ሥራ አስኪያጅ ፍሬህይወት መኮንን እንደገለፁት አየር መንገዱ ወደ ናይጄሪያ እና ከናይጄሪያ ወደ ሌሎች ሀገራት የሚደረገውን ቱሪዝም የማስተዋወቅ ጥረቱን ያጠናክራል ብለዋል።
"የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ንግድ እና ቱሪዝም አገናኝ ነው። ከዓለም ዙሪያ ወደ ናይጄሪያ ተጨማሪ ቱሪዝም ለመሳብ እንዲሁም ናይጄሪያውያን ኢትዮጵያን እና ሌሎች የአፍሪካ ክፍሎችን እንዲጎበኙ ለማበረታታት ቁርጠኛ ነን" ብለዋል ሲል የናይጄሪያ ሚዲያ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካላባር ካርኒቫልን ጨምሮ ዋና ዋና የናይጄሪያ ባህላዊ ዝግጅቶችን በተከታታይ በመደገፍ የቅናሽ ዋጋዎችን እና እንከን የለሽ የጉዞ አማራጮችን አቅርቧል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X