ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር ያላት ኢኮኖሚያዊ ግኑኝነት እየተጠናከረ እንደመጣ ገለፀች
19:44 04.05.2025 (የተሻሻለ: 20:04 04.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር ያላት ኢኮኖሚያዊ ግኑኝነት እየተጠናከረ እንደመጣ ገለፀች
ግኑኝነቱ በኢንቨስትመንት እና በወጪ ንግድ ከግዜ ግዜ እያደገ መጥቷል ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ደኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ሆኖም የሁለቱ ሀገራት የንግድ ትስስር ይበልጥ መዳበር እንደሚችል አንስተዋል።
"ማዳበሪያ ከሩሲያ ማምጣት እንችላለን፤ ሀገር ውስጥ የማይመረት ምርት ስለሆነ። አንዳንድ ማሽነሪዎችን፣ መኪኖችን ከሩሲያ የማምጣት እድሎች አሉ" ብለዋል።
ሀገሪቱ ከብሪክስ አባላት በተለይም ከሩሲያ፣ ቻይና እና ብራዚል ጋር የተሻለ የወጪ እና የገቢ ንግድ ግኑኝነት እንዳለትና የገበያ እድሎችን መፈለጓን አጠናክራ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X