ኢትዮጵያ በተኪ ምርቶች ያስመዘገበችው ስኬት አበረታች ነው ተባለ
18:07 04.05.2025 (የተሻሻለ: 18:24 04.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በተኪ ምርቶች ያስመዘገበችው ስኬት አበረታች ነው ተባለ
መንግሥት ሀገር ውስጥ ለሚመረቱ ምርቶች ቅድሚያ በመሥጠት ግዢ እየፈፀመ ነው ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ደኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ይህም አምራቾች ተኪ ምርትን እንዲያመርቱ እያበረታታቸው ነው ብለዋል።
በዚህም በዘጠኝ ወር ውስጥ ብቻ 3.1 ቢሊዮን ዶላር ሀገር ውስጥ ማስቀረት እንደተቻለ ገልጸዋል።
አክለውም 96 የሚጠጉ ምርቶችን በመለየት በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ግዜ ውስጥ ለመተካት ስትራቴጂ መነደፉን አስታውቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X