የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ለዩክሬን 310 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የF-16 መሳሪያ ሽያጭ ማፅደቁን ፔንታጎን ገለፀ
15:58 03.05.2025 (የተሻሻለ: 16:14 03.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ለዩክሬን 310 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የF-16 መሳሪያ ሽያጭ ማፅደቁን ፔንታጎን ገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ለዩክሬን 310 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የF-16 መሳሪያ ሽያጭ ማፅደቁን ፔንታጎን ገለፀ
ስምምነቱ የአውሮፕላን ማሻሻያዎችን፣ ሥልጠና፣ መለዋወጫ ዕቃዎችን እና የመሬት ላይ አገልግሎት መሣሪያዎችን ማቅረብ ያካትታል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ታሚ ብሩስ ዩናይትድ ስቴትስ በአሁኑ ጊዜ ዩክሬንን "የመተው" ፍላጎት የላትም ብለዋል።
አሜሪካ በትራምፕ እና በዘለንስኪ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት በመጋቢት ወር መጀመሪያ ለዩክሬን የምታደርገውን ወታደራዊ እርዳታ አቋርጣ ነበር። ሆኖም መጋቢት 10 በተደረገው ስብሰባ ዩክሬን የኃይል ማመንጫ ተቋማት ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለ30 ቀናት ለማቆም ከተስማማች በኋላ ድጋፏን ቀጥላለች። ኪዬቭ ይህን ስምምነት ከ140 ጊዜ በላይ ጥሳለች።
ሩሲያ ለዩክሬን የሚላኩ የምዕራባውያን የጦር መሳሪያዎች የሰላም ሂደት እንደሚያደናቅፉ እና የኔቶ አባል ሀገራትን የግጭቱ አካል እንደሚያደርጉ ደጋግማ ትናግራለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X