የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሃፊ በድርጅቱ ማሻሻያ ዙሪያ በቅርቡ ለአባል ሀገራት ሀሳቦችን እንደሚያቀርቡ ተገለፀ
13:48 03.05.2025 (የተሻሻለ: 14:04 03.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሃፊ በድርጅቱ ማሻሻያ ዙሪያ በቅርቡ ለአባል ሀገራት ሀሳቦችን እንደሚያቀርቡ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሃፊ በድርጅቱ ማሻሻያ ዙሪያ በቅርቡ ለአባል ሀገራት ሀሳቦችን እንደሚያቀርቡ ተገለፀ
ይህም በጥቂት ሳምንታት ውስጥ እንደሚሆን የተመድ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪክ ለሚዲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
እንደ ቃል አቀባዩ ገለጻ የማሻሻያ ሃሳቡ በሚከተሉት ጉዳዮች ዙሪያ ያተኩራል፦
⦁ የሀብት አጠቃቀምን ማሻሻል፣
⦁ ኃላፊነትን መልሶ ማደራጀት፣
⦁ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስርዓት ውስጥ መዋቅራዊ ለውጥ ማድረግ።
አንቶኒዮ ጉተሬዝ የተመድ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ የወጪ ቅነሳን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮግሞችን መጋቢት ወር ላይ ይፋ አድርገዋል። ማሻሻያው የትራምፕ አሜሪካ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምታደርገውን የገንዘብ ድጋፍ እየቀነሰች ባለበት ጊዜ የመጣ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X