ኢትዮጵያ የቡና ቱሪዝም ፓኬጆችን ማዘጋጀት ጀመረች
11:09 03.05.2025 (የተሻሻለ: 11:24 03.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የቡና ቱሪዝም ፓኬጆችን ማዘጋጀት ጀመረች
እቅዱ ሀገሪቱ የቡና ምንጭ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ ከዘርፉ ተጠቃሚነቷን ለማረጋገጥ በማሰብ የተዘጋጀ ነው።
ቡና ከኢኮኖሚያዊ ጥቅሙ ባለፈ የተለየ ባህላዊ ዋጋ አለው ያሉት የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ፤ መሥሪያ ቤታቸው ከቡና ማሕበራት ጋር በመተባበር ለጎብኚዎች የሚሆኑ ፓኬጆችን እያዘጋጀ እንደሆነ ገልጸዋል።
የቡና በቀላ፣ ለቀማ እና ሁሉንም የቡና ማቀነባበሪያ ሂደቶች እንዲሁም ደማቅ የቡና ባህል ሥነ-ሥርዓቶችን ያካትታል መባሉን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ ቡና ዘርፍ ከ25 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የኑሮ መሠረት እንደሆነም ተነግሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X