የኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ ለሀገር በቀል እውቀት እና ለብሪክስ ትብብር ቅድሚያ ይሰጣል ሲሉ ዳይሬክተሩ ተናገሩ

የኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ ለሀገር በቀል እውቀት እና ለብሪክስ ትብብር ቅድሚያ ይሰጣል ሲሉ ዳይሬክተሩ ተናገሩ
ለስፑትኒክ አፍሪካ ልዩ ቃለ መጠይቅ የሰጡት የኢትዮጵያ የሳይንስ አካዳሚ ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ተከተል ዮሐንስ አካዳሚው በቅርቡ "የኢትዮጵያ በእውቀት ላይ የተመሠረተ ኢኮኖሚ" የተሰኘ መጽሐፍ እንደሚያወጣ ገልጸዋል። መጽሐፉ ስለ ሀገር በቀል እውቀት የሚዳስስ ምዕራፍ ይኖረዋል ብለዋል።
ዳይሬክተሩ ሀገር በቀል እውቀት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ፅሑፍ ለማዘጋጀት እቅድ እንዳለም ተናግረዋል። የትምህርት እና የኢኖቬሽን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች በጉዳዩ ዙረያ ዳይሬክቶሬቶችን ለማቋቋም ጥረት እያደረጉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ምሑሩ አካዳሚው ከብሪክስ ጋር ስላለው ተሳትፎም አንስተዋል። በብራዚል ስለሚካሄደው የብሪክስ አካዳሚ ስብሰባ እና አካዳሚው በአዲስ አበባ በተካሄደው የብሪክስ ሳይንስ ኔትወርክ ወርክሾፕ ላይ መሳተፉን ጠቅሰዋል።
"በብሪክስ ጥላ ሥር የተጀመሩት ትብብሮችና ትስስሮች ይበልጥ መጠንከር አለባቸው" ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ በሩሲያ አስተማሪዎች የኬሚስትሪ ትምህርት ስለመማራቸው ያስታወሱት ፕሮፌሰር ዮሐንስ፤ የብሪክስ ትብብር ሳይንሳዊ ጥረቶች አሁን ካሉበት የጅማሮ ደረጃ ለማሳደግ አቅም ይሰጣል ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል። ውይይቶች ወደ ተጨባጭ እርምጃ እና ትግበራ መቀየር አለባቸው ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X