የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሥነ ምህዳርን በመጠበቅ ረገድ ቁልፍ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው
21:54 02.05.2025 (የተሻሻለ: 22:14 02.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሥነ ምህዳርን በመጠበቅ ረገድ ቁልፍ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሥነ ምህዳርን በመጠበቅ ረገድ ቁልፍ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው
ግድቡ የሀገር በቀል እፅዋት እንዲለመልሙ እያደረገ እና ከዚህ በፊት የተራቆቱ አካባቢዎችን እያለመ እንደሆነ ይነገራል።
ተጨማሪ የግድቡ ጥቅሞች፦
የኤሌክትሪክ ኃይል፦ ግድቡ ከ6 ሺህ ሜጋ ዋት በላይ ኤሌክትሪክ በማመንጨት በአፍሪካ ግዙፉ የውሃ ኃይል ማመንጫ ይሆናል።
የተጣራ ውሃ፦ ህዳሴ የብሉ ናይልን የደለል ፍሰት በመቀነስ ንፁህ እና የታችኞቹ ተፋሰስ ሀገራት ለመቆጣጠር የሚችሉት ውሃ እንዲደርሳቸው ከማስቻል ባለፈ የመስኖ እና የውሃ ጥራትን ያሻሽላል።
ጎርፎችን ማረጋጋት፦ ወቅታዊ ጎርፎችን በመቆጣጠር ተደጋጋሚ ጉዳቶችን ይከላከላል።
የዓሳ ምርት እና ሥራ ፈጠራ፦ ግድቡ ከወዲሁ ከፍተኛ የሆነ የዓሣ ምርት እየሰጠ ሲሆን በሥራ ፈጠራ የአካባቢውን ኢኮኖሚ በመደገፍ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል።
አዲስ የቱሪዝም መዳረሻ፦ በአካባቢው እየታየ ያለው የሥነ-ምህዳር ለውጥ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ጎብኚዎችን የሚስብ የቱሪስት መዳረሻ ያደርገዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X