የናይጄሪያ የፌዴራል ኮሌጆች ድርብ የምስክር ወረቀት መስጠት ሊጀምሩ ነው
18:57 02.05.2025 (የተሻሻለ: 19:14 02.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ የፌዴራል ኮሌጆች ድርብ የምስክር ወረቀት መስጠት ሊጀምሩ ነው
ተማሪ ቤቶቹ ከመስከረም 2018 ዓ.ም ጀምሮ የናይጄሪያን የትምህርት ሰርተፍኬት እና የመጀመሪያ ዲግሪ መስጠት ይጀምራሉ። ለውጡ ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኑቡ በፈረንጆቹ 2023 በኮሌጆች የአስተዳደር ሕግ ላይ ማሻሻያ ማድረጋቸውን ተከትሎ የመጣ ነው።
ፕሮግራሙ የተመራቂዎችን ሥራ የማግኘት ዕድል የማሳደግ እና የከፍተኛ ትምህርትን የማጠናከር ውጥን አንግቧል።
ተነሳሽነቱ መንግሥት በትምህርት ዘርፉ የሚያካሂደው ማሻሻያ ቁልፍ አካል ሲሆን በናይጄሪያ የከፍተኛ ትምህርት ስርዓት ላይ ጥራት እና ተፈላጊነትን ለማምጣት ያለመ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X