በ2025 ከፍተኛ ዕድገት ያስመዘግባሉ ተብለው የሚጠበቁ 10 የከሰሃራ በታች ሀገራት
15:24 02.05.2025 (የተሻሻለ: 15:44 02.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በ2025 ከፍተኛ ዕድገት ያስመዘግባሉ ተብለው የሚጠበቁ 10 የከሰሃራ በታች ሀገራት
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ከሰሃራ በታች ላሉ የአፍሪካ ሀገራት ባወጣው ክልላዊ የኢኮኖሚ ምልከታ የሚከተሉት ሀገራት በ2025 ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት ያስመዘግባሉ ተብሎ ይጠበቃል፦
ሴኔጋል: 8.4%
ጊኒ: 7.1%
ሩዋንዳ: 7.1%
ኒጀር: 6.6%
ኢትዮጵያ: 6.6%
ቤኒን: 6.5%
ኮትዲቯር: 6.3%
ኡጋንዳ: 6.1%
ዛምቢያ: 6.2%
ታንዛኒያ: 6.0%
የሳህል ሀገራት ጥምረት አባል የሆነችው ኒጀር የነዳጅ ምርቷ መጨመሩን ተከትሎ በ2024 ኢኮኖሚያዋ በ10.3% አድጎ የአህጉሪቱን የተሻለ አፈጻጸም አስመዝግባለች። ሌሎች የጥምረቱ አባላት ቡርኪናፋሶ እና ማሊ በበኩላቸው በቅደም ተከተል 4.3% እና 4.9% የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት ያስመዘግባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በአጠቃላይ አይኤምኤፍ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የጂዲፒ ዕድገት በ2024 ከነበረው 4.0% በ2025 ወደ 3.8% ዝቅ እንደሚል እና በ2026 ወደ 4.2% ከፍ እንደሚል ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X