ኮንጎ እና ሩዋንዳ በሁለት ወራት ውስጥ የሰላም ስምምነት ይፈራረማሉ ብላ አሜሪካ እንደምትጠብቅ ዘገባዎች አመላከቱ
13:08 02.05.2025 (የተሻሻለ: 13:14 02.05.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኮንጎ እና ሩዋንዳ በሁለት ወራት ውስጥ የሰላም ስምምነት ይፈራረማሉ ብላ አሜሪካ እንደምትጠብቅ ዘገባዎች አመላከቱ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኮንጎ እና ሩዋንዳ በሁለት ወራት ውስጥ የሰላም ስምምነት ይፈራረማሉ ብላ አሜሪካ እንደምትጠብቅ ዘገባዎች አመላከቱ
የፕሬዝዳንት ትራምፕ ከፍተኛ የአፍሪካ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ለምዕራባውያን ሚዲያዎች እንደገለጹት ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና ሩዋንዳ ከሰላም ስምምነቱ በተጨማሪ ከዩናይትድ ሰትቴስ ጋር በተናጠል የማዕድን የመግባቢያ ሰነድ ዋሽንግተን ውስጥ ይፈራረማሉ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በግንቦት ወር አጋማሽ የሰላም ስምምነቱን ለማጠናቀቅ ከሩዋንዳ እና ኮንጎ አቻዎቻቸው ጋር እንደሚገናኙ ቡሎስ ጨምረው ገልጸዋል።
አክለውም አሜሪካ፣ ኳታር፣ ፈረንሳይ እና ቶጎን (የአፍሪካ ህብረትን በመወከል) ያካተተ የክትትል ቡድን መመሥረቱን አስታውቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X