የሠራተኞች የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ትግል ሲታወስ!
16:41 01.05.2025 (የተሻሻለ: 17:04 01.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሠራተኞች የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ትግል ሲታወስ!
የአፍሪካ ሠራተኞች ኢኮኖሚን ከመገንባት ባለፈ ቅኝ አገዛዝን ታግለዋል ሲሉ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፈደሬሽን ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ከዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀን ጋር በተያያዘ ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት ቃል አስታውሰዋል።
የሠራተኛ ንቅናቄዎች ብዝበዛን በመቃወም እና ብሔራዊ ሉዓላዊነትን በማስመለስ ረገድ ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል ብለዋል።
"የአፍሪካ ሠራተኞች ቅኝ ገዢዎችን ለመጣል ታግለዋል...በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ብዙ አስተዋፅኦ አድርገዋል" ሲሉ ተናግረዋል።
ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንመለከት የሠራተኞች ቀን በኢትዮጵያ ትልቅ ቦታ ነበረው። እንደ አቶ ካሳሁን ገለጻ በሀገሪቱ የሠራተኞች ግንዛቤን፣ እውቀት እና የኢንዱስትሪ መስፋፋትን በማሳደግ ረገድ ጉልህ አስተዋፅኦ አድርጓል።
ስለ አሁናዊ ትግሎች ሲናገሩ "አፍሪካውያን የሲቪል ማሕበረሰቡን እና ሚዲያውን ማነቃነቅ አለባቸው። አፍሪካን ከውጭ ሆናችሁ ለማጠናከር አትጠብቁ" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
አክለውም እንደ ብሪክስ ያሉ ጥምረቶች የአፍሪካ ሠራተኞችን በገበያ ተደራሽነት፣ በኢንዱስትሪ መሠረተ ልማት እና አቅም ግንባታ ለመደገፍ ያላቸውን አቅም ጠቁመዋል። በአግባቡ ከተያዙ እነዚህ አጋርነቶች "በኢትዮጵያ የተሻሻሉ ደረጃዎች እና ጥበቃ የሚያስገኙ የሥራ እድሎችን ሊፈጥሩ ይችላሉ" ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X