በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እና ትልቁ ከባዮጋዝ ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ ፕሮጀክት ተመረቀ
11:49 01.05.2025 (የተሻሻለ: 12:04 01.05.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እና ትልቁ ከባዮጋዝ ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ ፕሮጀክት ተመረቀ
300 ሜትር ኪዩብ የማብለያ አቅም ያለው ሲሆን 20 ኪሎ ዋት ሀወር ኃይል ያመርታል።
በዓመት 87 ሺህ 600 ኪሎ ዋት ሀወር ኃይልን በመቆጠብ 12 ሚሊየን 950 ሺህ ብር የሚጠጋ ወጪን እንደሚቆጥብ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ፕሮጀክቱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከቻይና መንግሥት፣ ከዩኤን ዲፒ እና ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር እንዳስገነቡት ተገልጿል።
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የተገነባው የባዮጋዝ ኤሌክትሪክ ማመንጪያ የተቋሙን የማብሰል ሂደት መሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚተካ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X