ኢትዮጵያ የብሪክስ ሀገራት ነገሮችን በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት እያደረጉት ያለውን ጥረት አደነቀች
11:07 29.04.2025 (የተሻሻለ: 15:44 29.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ የብሪክስ ሀገራት ነገሮችን በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት እያደረጉት ያለውን ጥረት አደነቀች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የብሪክስ ሀገራት ነገሮችን በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት እያደረጉት ያለውን ጥረት አደነቀች
ኢትዮጵያ በብራዚል እየተካሄደ ባለው የብሪክስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ እየተሳፈች ነው።
በስብሰባው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ኢትዮጵያ ለባለብዙወገን ግንኙነት እና የጋራ ደኀንነት ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።
አክለውም የዓለም አስተዳደር አዳጊ ሀገራትን በተለይም አፍሪካን ባማከለ ፍትሐዊ ውክልና እንዲኖር ማሻሻያዎች መደረግ እንዳለባቸው አጽዕኖት ሰጥተዋል።
ሚኒስትሩ የሚደረጉ ማሻሻያዎች የባለብዙ ወገን ግንኙነትን የሚያጠናክር እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ማዕከል ያደረገ መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል።
የብሪክስ ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ በዛሬው ዕለት ሲቀጥል በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚመክር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X