ኢትዮጵያ ትምህርት እና ቴክኖሎጂን ማዕከል አድርጋ እየሠራች እንደሆነ ገለጸች
12:35 28.04.2025 (የተሻሻለ: 12:54 28.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ትምህርት እና ቴክኖሎጂን ማዕከል አድርጋ እየሠራች እንደሆነ ገለጸች
በኢትዮጵያ የሚካሄደው የኢኖቬሽን አፍሪካ 2025 የሚኒስትሮች ስብሰባ ዛሬ ተከፍቷል፡፡
መድረኩን የከፈቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በኢትዮጵያ የአዳዲስ ትምህርት ቤቶች ግንባታ፣ የተሻሻሉ መሠረተ ልማቶች እና ጠንካራ የዲጂታል ትስስር እየተዘረጋ ይገኛል ብለዋል፡፡
በአፍሪካ አሁንም የትምህርት እና የዲጂታላይዜሽን ጉዞን በማሳካት በኩል ቀሪ ሥራዎች አሉ ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ለነገው ትውልድ የምናደርገውን የትምህርት እና የቴክኖሎጂ ኢንቨስትመንት በተቀናጀ እና በተቀላጠፈ መልኩ ማከናወን ይገባናል” ሲሉ ተናግረዋል።
መድረኩ በትምህርት፣ በኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽንና በአቅም ግንባታ ላይ ያተኩራል ተብሏል።
በስፑትኒክ ዘጋቢ የተነሱ ምስሎች
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
