በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 7.5 ቢሊየን ችግኝ ለመተክል መታቀዱ ተነገረ
12:14 28.04.2025 (የተሻሻለ: 12:34 28.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር 7.5 ቢሊየን ችግኝ ለመተክል መታቀዱ ተነገረ
ዘንድሮ በሚካሄደው ተከላ ለሀገር በቀል የደን እና የፍራፍሬ ችግኞች ትኩረት ይሰጣል።
ለመርሃ-ግብሩ ከሚለየው መሬት 50 በመቶ ለሚሆነው ካርታ እንደሚዘጋጅ የኢትዮጵያ ደን ልማት አስታውቋል።
በበጋው ወራት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ የተሠራባቸው፣ የተራቆቱ እንዲሁም ለዚሁ አገልግሎት የተዘጋጁ ቦታዎች በአረንጓዴ አሻራው ፕሮግራም ተካተዋል።
ኢትዮጵያ በሁለተኛው ምዕራፍ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር 50 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል አቅዳለች፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X