የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከብራዚል አቻቸው ጋር ተወያዩ
11:49 28.04.2025 (የተሻሻለ: 12:04 28.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከብራዚል አቻቸው ጋር ተወያዩ
የሁለቱ ሚኒስትሮች ውይይት የተካሄደው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ከመካሄዱ አስቀድሞ መሆኑ ተጠቅሷል።
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ሰርጌ ላቭሮቭ እና ማውሮ ቪዬራ በበርካታ ዘርፎች የሁለትዮሽ ትብብር፣ የብሪክስ እና ዓለም አቀፍ መድረኮች እንዲሁም የዩክሬንን ግጭት ማቆምን በተመለከተ ተወያይተዋል።
ሚኒስቴሩ አክሎም የብራዚል ፕሬዝዳንት ሉላ ዳ ሲልቫ በታላቁ የአርበኝነት ጦርነት ድል 80ኛ ዓመት መታሰቢያ ላይ ስለሚኖራቸው ተሳትፎ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን አሳውቋል።
ላቭሮቭ የቡድኑን ስምምነቶች በተግባር ላይ በማዋል እና ስትራቴጂካዊ ጥምረቶችን ለማጠናከር እቅዶችን በማውጣት ላይ በሚያተኩረው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ በትላንትናው ዕለት ብራዚል ገብተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
