ለሶማሊያ ሰላም እና መረጋጋት የአፍሪካውያን የጋራ ትብብር ወሳኝ እንደሆነ ኢትዮጵያ አስገነዘበች
12:57 26.04.2025 (የተሻሻለ: 13:14 26.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱለሶማሊያ ሰላም እና መረጋጋት የአፍሪካውያን የጋራ ትብብር ወሳኝ እንደሆነ ኢትዮጵያ አስገነዘበች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ለሶማሊያ ሰላም እና መረጋጋት የአፍሪካውያን የጋራ ትብብር ወሳኝ እንደሆነ ኢትዮጵያ አስገነዘበች
በአፍሪካ ሕብረት የድጋፍና የማረጋጋት ተልዕኮ በሶማሊያ ሥር ወታደሮች ያዋጡ ሀገራት የሰላም አስከባሪ ኃይሉን ቁጥር በትንሹ በ8 ሺህ ከፍ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአጋንዳ የተካሄደውን ስብሰባ ተከትሎ ባወጡት የጋራ መግለጫ በሶማሊያ እየጨመረ የመጣው የደህንነት ስጋት በሀገሪቱ ስርዓት በመመለስ ረገድ የተገኘውን ስኬት እንዳያከሸፍ መተባበር እንደሚገባ አስረግጠዋል።
በጉባዔው የኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ጂቡቲ እና ሶማሊያ የመከላከያ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተሳትፈዋል።