የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በቀጣዩ የበጀት ዓመት ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንደሚል የሀገሪቱ ማዕከላዊ ባንክ አስታወቀ
12:37 25.04.2025 (የተሻሻለ: 12:54 25.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በቀጣዩ የበጀት ዓመት ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንደሚል የሀገሪቱ ማዕከላዊ ባንክ አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት በቀጣዩ የበጀት ዓመት ወደ 10 በመቶ ዝቅ እንደሚል የሀገሪቱ ማዕከላዊ ባንክ አስታወቀ
የባንኩ አስተዳዳሪ ማሞ ምሕረቱ ትናንት በዋሽንግተን በተካሄደው የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትና ዓለም ባንክ ስብሰባ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የዋጋ ግሽበቱ በመጋቢት ወር 13 በመቶ መደረሱን ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ በእጥፍ ያድጋል ብለው እንደሚጠብቁ እና ከውጭ የሚላክ ገንዘብ በትንሹ በ25 በመቶ ሊጨምር እንደሚችልም ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡
በተጨማሪም የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ከፍተኛ እድገት ማሳያቱን አስታውቀዋል፡፡
"ከማሻሻያው በኋላ የውጭ ምንዛሪ ክምችታችን በሦስት እጥፍ ጨምሯል። በባንክ ሥርዓቱ ያለው ክምችት በእጥፍ ጨምሯል፡፡ በኢኮኖሚው የካፒታል ፍሰት ላይ ግልፅ እድገት እና ጥንካሬ ይታያል" ብለዋል።