ከአዲስ አበባ የሚመነጩ ቆሻሻዎች ወደ ታዳሽ ኃይል ሊቀየሩ ነው
16:05 24.04.2025 (የተሻሻለ: 16:24 24.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ከአዲስ አበባ የሚመነጩ ቆሻሻዎች ወደ ታዳሽ ኃይል ሊቀየሩ ነው
ከአዲስ አበባ መንጭተው ረጲ አካባቢ የሚጣሉ ቆሻሻዎችን ወደ ኢኮ ፓርክነት የሚቀይር እና የኃይል አማራጭን በማስፋት ተጨማሪ ገቢ ያስገኛል የተባለ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈርሟል፡፡
ስምምነቱ የተፈረመው በቻይና ሻንዥን ኢነርጂ ግሩፕ፣ የቻይና ብሔራዊ ኤሌክትሪክ ኢንጅነሪንግ ድርጅት እና በጀርመኑ ኮቬናንት ኢንጅነሪንግ ድርጅት መካከል ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ከተማዋን ውብ እና ፅዱ እንዲሁም ስማርት ሲቲ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትን የሚያግዝ ነው መባሉን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።