ሩሲያ የአፍሪካን አቋም በማጠናከር ረገድ እገዛ እንደምታደርግ ላቭሮቭ ተናገሩ
21:31 23.04.2025 (የተሻሻለ: 22:34 23.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ የአፍሪካን አቋም በማጠናከር ረገድ እገዛ እንደምታደርግ ላቭሮቭ ተናገሩ
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሞስኮ አፍሪካ በአዲሱ ዓለም አቀፍ ሥርዓት ውስጥ ነጻ ተዋናይ እንድትሆን ለመርዳት ቁርጠኛ ነች ብለዋል።
ላቭሮቭ ሩሲያ ለአፍሪካ ልማት ያላት ቁርጠኝነት
🟠 በሉዓላዊነት፣
🟠 በትምህርት፣
🟠 በላቁ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽነት ላይ ያተኮረ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ሩሲያ ለአፍሪካ የነጻነት ንቅናቄዎች ያደረገችውን ድጋፍ በማስታወስ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ታሪካዊ የወዳጅነት ትስስር አጉልተዋል።
ላቭሮቭ አክለውም ሩሲያ እና የአፍሪካ አጋሮቿ አዲስ ቅኝ አገዛዝን ለመቃወም እና ገለልተኛ የኢኮኖሚ መፍትሄዎችን ለመመስረት በጋራ እየሠሩ መሆናቸውን አንስተዋል።