ቻይና እና ኬንያ በናይሮቢ አዲስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕንፃ ለመገንባት ተስማሙ
16:28 23.04.2025 (የተሻሻለ: 16:54 23.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቻይና እና ኬንያ በናይሮቢ አዲስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሕንፃ ለመገንባት ተስማሙ
ስምምነቱ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ወደ ቻይና የሥራ ጉብኝት ማደረግ ከመጀመራቸው ጋር ተያይዞ የተገለጸ ነው፡፡ ሩቶ ከቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በርካታ ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ስምምነቶችን ይፈርማሉም ተብሎ ይጠበቃል።
የፕሮጀክቱ ዝርዝር ጉዳዮች፦
🟠 ግንባታው የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሥራዎች እየሰፉ በመምጣታቸው አስፈላጊ ሆኖ እንደተገኘ ተገልጿል፣
🟠 ቻይና የሁለቱን ሀገራት የ60 ዓመታት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን አስመልክቶ የተወሰነውን ገንዘብ ትሸፍናለች፣
🟠 የፕሮጀክቱ የአዋጭነት ጥናት እየተካሄደ በመሆኑ የግንባታው ትክክለኛ ወጪ እስካሁን ይፋ አልተደረገም።