በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ የሽብር ጥቃት በማክሸፍ ያሰለጠናቸውን ሙያተኞች አስመረቀ
15:43 23.04.2025 (የተሻሻለ: 16:04 23.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ የሽብር ጥቃት በማክሸፍ ያሰለጠናቸውን ሙያተኞች አስመረቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሶማሊያ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ የሽብር ጥቃት በማክሸፍ ያሰለጠናቸውን ሙያተኞች አስመረቀ
ስልጠናው በሶማሊያ በድጋፍ ሰጪነት ተሰማርተው ለሚገኙ የምስራቅ ዕዝ አንድ ኮር አባላት እንደተሰጠ ተገልጿል። ከተባበሩት መንግሥታት የፈንጂ እርምጃ አገልግሎት ጋር በመተባበር የተሰጠው ስልጠና የንድፈ-ሀሳብ እና የተግባር ስልጠናን ያካተተ እንደነበር የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።
የሴክተር አራት ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ሹመት ጠለለው ሙያተኞቹ ከስልጠናው ባገኙት እውቀት የተሰጣቸውን ተልእኮ በብቃት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።
"በየጊዜው ቴክኖሎጂዎች እየተሻሻሉ በመጡ ቁጥር ብዙ አማራጮች ይኖራሉ። ከግዳጅ ቀጣናው ጋር ተያይዞ አልሻባብ በዋናነት የሚጠቀምባቸውን ፈንጆች በመለየት እና ፍተሻዎችን በማድረግ ጉዳት ሳያደርሱ ማስወገድ ቀዳሚው ተግባር ነው" ሲሉ አሳስበዋል።