የሩሲያ መንግሥት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ ላብራቶሪ ለኢትዮጵያ ለገሰ
12:55 23.04.2025 (የተሻሻለ: 16:44 23.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ መንግሥት ዘመናዊ ተንቀሳቃሽ ላብራቶሪ ለኢትዮጵያ ለገሰ
ላብራቶሪውን የሩሲያ የሸማቾች መብት እና የዜጎች ደህንነት ጥበቃ ኤጀንሲ ኃላፊ ዶክተር አና ፖፖቫ ለኢትዮጵያ ጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ አስረክበዋል።
ሩሲያ ሰር የሆነው ይህ ላብራቶሪ "በሽታን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል" አስተዋጽኦ ያደርጋል ሲሉ ኃላፊዋ ዶክተር አና ፖፖቫ በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተናግረዋል።
ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው ተንቀሳቃሽ ላቦራቶሪው የኢትዮጵያን የጤና ስርዓት በማጠናከር በተለይም ተላላፊ በሽታዎችን የመቋቋም አቅም በማጎልበት በኩል ጉልህ ሚና ይኖረዋል ማለታቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ጋዜጠኛ ዘግቧል።
የሕክምና መሳሪያው በአንድ ጊዜ 300 በሽታዎችን የመለየት አቅም እንዳለውም ጠቁመዋል።
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
