የጃፓኑ ቶዮ በኢትዮጵያ የገነባው የሶላር ማመረቻ ፋብሪካ ሥራ ጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየጃፓኑ ቶዮ በኢትዮጵያ የገነባው የሶላር ማመረቻ ፋብሪካ ሥራ ጀመረ
የጃፓኑ ቶዮ በኢትዮጵያ የገነባው የሶላር ማመረቻ ፋብሪካ ሥራ ጀመረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.04.2025
ሰብስክራይብ

የጃፓኑ ቶዮ በኢትዮጵያ የገነባው የሶላር ማመረቻ ፋብሪካ ሥራ ጀመረ

በሐዋሳ ከተማ በስልሳ ሚሊዮን ዶላር የተገነባው ፋብሪካ አሁን ላይ የማምረት አቅሙ 2 ጊጋዋት እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ኩባንያው በመጪው ነሐሴ የማምረት አቅሙን ወደ 4 ጊጋዋት እንደሚያሳድግ አስታውቋል።

በሚያዚያ ወር መጨረሻ ኩባንያው ከ80 ሜጋዋት በላይ የፀሐይ ሴሎችን ወደ ውጭ ይላካል ተብሎ እንደሚጠበቅ አሳውቋል።

የቶዮ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጁንሴይ ሪዩ  "በገበያው ላይ ባየነው ጠንካራ ፍላጎት በጣም ደስተኞች ነን፡፡ በኢትዮጵያ የ2 ጊጋዋት የማስፋፊያ ሥራ ለመተግበር በትጋት እየሠራን ነው" ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በቬትናም የቶዮ ኩባንያ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ማምረቻ ፋብሪካን በጎበኙበት ወቅት ኩባንያው በኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍ በስፋት እንዲሳተፍ ማበረታታቸው ይታወሳል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0