የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለካሜሩን ሃጅ ተጓዦች የተቀላጠፍ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት ገለፀ
11:22 23.04.2025 (የተሻሻለ: 11:44 23.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ አየር መንገድ ለካሜሩን ሃጅ ተጓዦች የተቀላጠፍ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት ገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለካሜሩን ሃጅ ተጓዦች የተቀላጠፍ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት ገለፀ
በካሜሩን የግዛት አስተዳደር ሚኒስትርና የሃጅ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች ጎብኝቷል።
ልዑኩ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ጋር ፍሬያማ ውይይት እንዳካሄደ አየር መንገዱ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ ያወጣው መረጃ ያሳያል።
በውይይቱ ወቅት አየር መንገዱ ከካሜሩን ለሚመጡ የሃጅ ተጓዦች አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጧል። በተጨማሪም ወደ ያውንዴ እና ዱአላ የሚያደርገውን መደበኛ በረራ የበለጠ አጠናከሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።