ሩሲያ ወደ ኢትዮጵያ የምታቀርባቸውን ምርቶች በዓይነትም ሆነ በመጠን ለመጨመር እየሠራች መሆኑ ተገለፀ
10:56 23.04.2025 (የተሻሻለ: 11:14 23.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ ወደ ኢትዮጵያ የምታቀርባቸውን ምርቶች በዓይነትም ሆነ በመጠን ለመጨመር እየሠራች መሆኑ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ ወደ ኢትዮጵያ የምታቀርባቸውን ምርቶች በዓይነትም ሆነ በመጠን ለመጨመር እየሠራች መሆኑ ተገለፀ
“በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ እያደገ ነው፤ በእኛ በበኩል የእቃዎችን ዓይነት ለማስፋትና የንግድ ዘርፉን ለማብዛት ያለማቋረጥ እየሠራን ነው” ሲሉ በኢትዮጵያ የሩሲያ የንግድ ተወካይ ያሮስላቭ ታራሲዩክ ከሩሲያ ኤክስፖርት ማዕከል እና ከሩሲያ ኢንዱስትሪና ንግድ ሚኒስቴር ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ከሩሲያ ኩባንያዎች ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኗን ጠቁመዋል።
እንደ ታራሲዩክ ገለጻ ለትብብር እና ወጪ ንግዱ ተስፋ ሰጪ ዘርፎች የሚከተሉት ናቸው፡-
🟠 የኤሌክትሪክ ኃይል
🟠 ትራንስፖርት
🟠 የግብርና-ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ
🟠 የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ
በተጨማሪም ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ትብብርን ማዳበር የሩሲያ ወጪ ንግድ ማዕከል ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ መሆኑን የድርጅቱ የትብብር መሠረተ ልማት ዳይሬክተር አርተር ዛቪያሎቭ ተናግረዋል።