ማርኮ ሩቢዮ ወደ ለንደን ሊያደርጉት የነበረውን ጉዞ ሰረዙ
10:10 23.04.2025 (የተሻሻለ: 10:34 23.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ማርኮ ሩቢዮ ወደ ለንደን ሊያደርጉት የነበረውን ጉዞ ሰረዙ
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ውሳኔ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ አሜሪካ ባቀረበችው ሀሳብ መሰረት ክራይሚያን የሩሲያ አካል አድርጎ ለመቀበል የቀረበውን ሃሳብ ውድቅ ካደረጉ በኋላ የመጣ ነው።
በተየያዘ ዜና የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን እና የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በለንደን ሊያደርጉት ያቀዱትን ስብሰባ ሳያራዝሙ እንዳልቀሩ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎች አመልክተዋል።
ይህም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ እና የትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ጉብኝታቸውን ከሰረዙ በኋላ የመጣ ነው።
ስቲቭ ዊትኮፍ በዚህ ሳምንት ለተጨማሪ ድርድር ወደ ሩሲያ ይጓዛሉ ተብሎ ይጠበቃል።