አዲስ አበባ የሚገኘው የሩሲያ ማዕከል የታላቁ ድል ባነር ቅጂን ተረከበ
12:39 22.04.2025 (የተሻሻለ: 13:14 22.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አዲስ አበባ የሚገኘው የሩሲያ ማዕከል የታላቁ ድል ባነር ቅጂን ተረከበ
እ.ኤ.አ ግንቦት 1 ቀን 1945 በርሊን በሚገኘው የሬይችስታግ ሕንፃ ጣሪያ ላይ በሬድ አርሚ ወታደሮች አሌክሲ ቤሬስት፣ ሚካሂል ኢጎሮቭ እና ሜሊተን ካንታሪያ የተሰቀለው ባነር የሶቪየት ጦር በናዚ ጀርመን ላይ የተቀዳጀው አስደናቂ ድል ምልክት ነው።
የሰንደቁን ቅጂ በኢትዮጵያ የሕያው ክፍለ ጦር አስተባባሪ ኤሌና ኃይሉ ሞስኮ በተካሄደ የታላቁ የአርበኝነት ጦርነት 80ኛ ዓመት መታሰቢያ መድረክ ላይ ከሶቪየት ሕብረት ጀግና ሚካሂል ኢጎሮቭ ሴት ልጅ ኢሪና ዶሮዝኪና እጅ ተቀበለዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሩሲያውያን፣ የሶቪየት እና የሩሲያ ዩኒቨርስቲ ምርቆች እንዲሁም የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ባነሩን በፑሽኪን አዳራሽ ማየት ይችላሉ።
@sputnik_ethiopia