የሩሲያ እና የሱዳን ኩባንያዎች በነዳጅ ምርት ዘርፍ አብረው ለመስራት ተስማሙ
15:10 21.04.2025 (የተሻሻለ: 15:44 21.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ እና የሱዳን ኩባንያዎች በነዳጅ ምርት ዘርፍ አብረው ለመስራት ተስማሙ
የመግባቢያ እና የትብብር ስምምነቱ በሩሲያዎቹ አል ራሲ ኢንተርናሽናል ሰርቪስ እና ዛሩቤዝኔፍት ድርጅቶች ከፍተኛ ተወካዩች እና በሱዳኑ ባሻየር ኦይል ፒፕላይንስ ድርጅት ተወካዩች መካከል ተፈርሟል። በፊርማ ሥነ-ሥረዓቱ ወቅት የሩሲያ ኤምባሲ ልዑካን በስፍራው መገኘታቸውን የሱዳን ኢነርጂ እና ፔትሮሊየም ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሁለቱ ወገኖች አክለውም በሚከተሉት ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፦
⏺ የመጨረሻ ስምምነት ማዘጋጀት፣
⏺ ከሱዳፔት ጋር አጋርነት መመስረት እና
⏺ ከሀገር ውስጥ ኩባንያዎች ጋር በነዳጅ ፍለጋ እና ምርት አገልግሎቶች ላይ ኢንቨስት ማድረግ።
@sputnik_ethiopia