ክሬምሊን ዩክሬን የፋሢካ ተኩስ አቁም ስምምነትን እንደጣሰች የሚያሳዩ መረጃዎችን ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱክሬምሊን ዩክሬን የፋሢካ ተኩስ አቁም ስምምነትን እንደጣሰች የሚያሳዩ መረጃዎችን ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ
ክሬምሊን ዩክሬን የፋሢካ ተኩስ አቁም ስምምነትን እንደጣሰች የሚያሳዩ መረጃዎችን ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.04.2025
ሰብስክራይብ

ክሬምሊን ዩክሬን የፋሢካ ተኩስ አቁም ስምምነትን እንደጣሰች የሚያሳዩ መረጃዎችን ይፋ እንደሚያደርግ አስታወቀ

ማስረጃው ማወቅ ለሚፈልጉ ወገኖች በሙሉ እንደሚቀርብ የሩሲያ ፕሬዚዳንታዊ ቃል አቀባይ ሰኞ እለት ተናግረዋል።

ሚያዚያ 11 ቀን በቭላድሚር ፑቲን የታወጀው የትንሣኤ ተኩስ አቁም ሚያዝያ 13 (በሞስኮ ሰዓት) እኩለ ሌሊት ላይ አብቅቷል። የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በኪዬቭ ኃይሎች 4 ሺህ 900 የተኩስ አቁም ጥሰት መፈጸሙን ሰኞ እለት አስታውቋል።

የዲሚትሪ ፔስኮቭ ተጨማሪ መግለጫዎች፡-

🟠 የትንሣኤ የተኩስ አቁም ፕሬዝዳንት ፑቲን በራሳቸው ተነሳሽነት ያወጁት ነበር።

🟠 ለሩሲያ ስጋት የሚፈጥር በመሆኑ ዩክሬን የኔቶ አባል መሆን የለበትም።

🟠 ዋሽንግተን በተለያዩ ግዜያት የዩክሬን የኔቶ አባልነት የማይቻል መሆኑን መግለጿ ከሞስኮ አቋም ጋር የሚጣጣም ነው።

🟠 ሩሲያ እና ዩናይትድ ስቴትስ በዩክሬን ጉዳይ የጀመሩት ግኑኝነት ውጤት ያስገኛል ብላ ሞስኮ ተስፋ ታደርጋለች።

🟠 ሩሲያ የዩክሬንን ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አሁንም ዝግጁ ነች።

🟠 የዩክሬን ሰላም ሂደት በአደባባይ ሊከናወን አይገባም። የመረጃ ፍሰት በጥንቃቄ መያዝ አለበት።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0