ኢትዮጵያ እና ኬንያ የሞያሌ ድንበር የንግድ ልውውጥን በ1 ሺህ ዶላር ጣሪያ ለመጀመር ተስማሙ
11:40 21.04.2025 (የተሻሻለ: 12:24 21.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ እና ኬንያ የሞያሌ ድንበር የንግድ ልውውጥን በ1 ሺህ ዶላር ጣሪያ ለመጀመር ተስማሙ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ኬንያ የሞያሌ ድንበር የንግድ ልውውጥን በ1 ሺህ ዶላር ጣሪያ ለመጀመር ተስማሙ
ይህ ስምምነት የመጣው ከሁለት ዓመታት ድርድር መሆኑ ተገልጿል። ሀገራቱ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ማዕቀፍ ስር የሁለትዮሽ የንግድ ልውውጥን ለማቀላጠፍ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነትም ተፈራርመዋል።
በስምምነቱ የኢትዮጵያ የድንበር ንግድ ዞን ከሞያሌ በ50 ኪሎ ሜትር እንዲሁም የኬንያ ደግሞ በ100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚወሰን ነው እንደሆነ ተዘግቧል።
ነጋዴዎችም በጋራ በተስማሙበት የምርት ዝርዝር መሰረት እስከ 1 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የንግድ ልውውጥ በወር እስከ አራት ጊዜ ድረስ ማካሄድ ይችላሉ።
@sputnik_ethiopia