ዴሞክራቶች የፓርቲውን ገጽታ ያበላሻል በማለት የጆ ባይደንን በአደባባይ መታየት እንደማይፈልጉ ሪፖርቶች አመላከቱ
13:26 20.04.2025 (የተሻሻለ: 13:44 20.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ዴሞክራቶች የፓርቲውን ገጽታ ያበላሻል በማለት የጆ ባይደንን በአደባባይ መታየት እንደማይፈልጉ ሪፖርቶች አመላከቱ
የዩናይትድ ስቴትስ ዴሞክራቲክ ፓርቲ አባላት የቀድሞው ፕሬዝዳንት እና ባለቤታቸው ጂል ባይደን የፓርቲውን ገጽታ እንዳያበላሹ በአደባባይ መገኘታቸው መገደብ እንዳለበት ያምናሉ ሲል የአሜሪካው ጋዜጣ ዘገበ።
" የባይደንን ቤተሰቦች በጣም እወዳቸዋለሁ፤ ነገር ግን የሰራተኞች ታማኝነት ማለት ሐቀኛ ሆነን በህዝብ ዘንድ ያላቸው ምስል ግንዛቤ እንዲኖራቸው የማድረግ ነው ፤ ምንም እንኳን ይህንን መስማት ጎጂ ቢሆንም" ሲሉ የጂል ባይደን የቀድሞ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሚካኤል ላሮሳ ለጋዜጣው ተናግረዋል።
ላሮሳ የንግድ ውድድር ፖሊሲ በተጧጧፈበት ወቅት የባይደን ወደ መድረኩ መመለስ "ለዋይት ሃውስ፣ ለፕሬዚዳንት ትራምፕ እና ለወግ አጥባቂ ሚዲያዎች የሚያምር ስጦታ ነው" ሲሉ ተከራክረዋል።
@sputnik_ethiopia