በሞልዶቫ ጳጳስ ላይ የተፈፀመው ድርጊት በምስራቅ አውሮፓ እና ሌሎችም አካባቢዎች የኦርቶዶክስ ክርስትናን ተፅዕኖ ለመቀነስ ከሚደረገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው ሲል ኢትዮጵያዊው ዘማሪ ተናገረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበሞልዶቫ ጳጳስ ላይ የተፈፀመው ድርጊት በምስራቅ አውሮፓ እና ሌሎችም አካባቢዎች የኦርቶዶክስ ክርስትናን ተፅዕኖ ለመቀነስ ከሚደረገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው ሲል ኢትዮጵያዊው ዘማሪ ተናገረ
በሞልዶቫ ጳጳስ ላይ የተፈፀመው ድርጊት በምስራቅ አውሮፓ እና ሌሎችም አካባቢዎች የኦርቶዶክስ ክርስትናን ተፅዕኖ ለመቀነስ ከሚደረገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው ሲል ኢትዮጵያዊው ዘማሪ ተናገረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.04.2025
ሰብስክራይብ

በሞልዶቫ ጳጳስ ላይ የተፈፀመው ድርጊት በምስራቅ አውሮፓ እና ሌሎችም አካባቢዎች የኦርቶዶክስ ክርስትናን ተፅዕኖ ለመቀነስ ከሚደረገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው ሲል ኢትዮጵያዊው ዘማሪ ተናገረ

የሞልዶቫ ኦርቶዶክስ ጳጳስ ለፋሲካ ወደ እየሩሳሌም እንዳይጓዙ መከልከላቸውን አስመልክቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ አስተያየቱን የሰጠው ጋዜጠኛ እና የኦርቶዶክስ ዘማሪ ሲኖዶስ ተስፋይ፤ የቅዱስ ብርሃን ሥነ-ሥርዓት በኦርቶዶክስ ክርስትና ትልቅ ቀን እንደሆነ እና ክልከላው ከተለመደው የኦርቶዶክስ እምነት እሴቶች መሸሽን የሚያመለክት ነው ብሏል።

"ጳጳሱ በሐይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓተ እንዳይገኙ መከልከል አሉታዊ መልዕክት የሚያስተላልፍ ነው። በእርግጠኝነት ለፖለቲካ ወይም የርዕዮተ ዓለም ምክንያቶች የተደረገ ነው። እርምጃው የሕዝቦችን፣ የአማኞችን እና የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን መብት የሚጥስ ነው" ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።

አክሎም ክልከላው ሰፋ ያለ ስትራቴጂ አካል ነው ብሏል።

"በሞልዶቫ ብቻ ሳይሆን፤ በምስራቅ አውሮፓ እና ሌሎችም አካባቢዎች የኦርቶዶክስ ክርስቲያኖችን ቁጥር የመቀነስ ስትራቴጂ ነው። በሞልዶቫ እንዲሁም በምስራቅ አውሮፓ ለኦርቶዶክስ ክርስትና አመቺ ያልሆኑ ሆኔታዎች መብዛታቸው በጣም አሳሳቢ ነው" ሲል ጨምሮ ገልጿል።

ሲኖዶስ ተስፋይ ሁኔታው ችላ ሊባል እንደማይገባም አስገንዝቧል።

"በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ተቃውሟቸውን እያሰሙ እንደሆነ አይቻለሁ። ይህ አግባብ ነው። አንድ ሆነን በቤተ-ክርስቲያኗ ላይ ተፅዕኖ እንዳይደረግ ማረጋገጥ" አለብን ሲል አፅንኦት ሰጥቷል።

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0