የጳጳስ ማርኬል የቅዱስ ጧፍ ጉዞ መስተጓጎል 'ሽብር' ነው ሲል የሞልዶቫ ተቃዋሚ ፓርቲ ገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየጳጳስ ማርኬል የቅዱስ ጧፍ ጉዞ መስተጓጎል 'ሽብር' ነው ሲል የሞልዶቫ ተቃዋሚ ፓርቲ ገለፀ
የጳጳስ ማርኬል የቅዱስ ጧፍ ጉዞ መስተጓጎል 'ሽብር' ነው ሲል የሞልዶቫ ተቃዋሚ ፓርቲ ገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 18.04.2025
ሰብስክራይብ

የጳጳስ ማርኬል የቅዱስ ጧፍ ጉዞ መስተጓጎል 'ሽብር' ነው ሲል የሞልዶቫ ተቃዋሚ ፓርቲ ገለፀ

የሞልዶቫ ሶሻሊስት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ "ይህ በሀገሪቱ ትልቁ የሐይማኖት ተቋም የሆነውን የሞልዶቫን ቀኖናዊ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ለማጣጣል እና ለማፈን ያለመ ሴራ ነው" ብሏል።

በፋሲካ ዋዜማ "ባለሥልጣናቱ ከሞልዶቫ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ሀገረ ስብከቶች መካከል የአንዱ መሪ የሆኑትን ሊቀ ጳጳስ በሕዝብ ፊት አዋርደዋል" ሲል ፓርቲው አስታውቋል።

መግለጫው አክሎም "ይህ የሥርዓቱ የሞራል ውድቀት ነው። ለዚህም ምንም ዓይነት ሥነ ምግባራዊ እና ሰብዓዊ ምክንያት ሊኖር አይችልም። ይህ ከብሔራዊ ማንነት ጋር ለረጅም ጊዜ ግንኙነቱን ያጣው ፀረ-ሕዝብ ሥርዓት በሞልዶቫ ኦርቶዶክሳዊ አብላጫ ላይ ያወጀው ጦርነት ነው" ብሏል።

የሞልዶቫ ካናል 5 የዜና ማሰራጫ እንደዘገበው ሊቀ ጳጳስ ማርኬል በቺሲናኡ አውሮፕላን ማረፊያ ታግደው፤ ጥልቅ ፍተሻ ከተደረገ በኋላ ወደ እስራኤል በሚጓዘው አውሮፕላን መሳፈር እንዳይችሉ ተከልክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

@sputnik_ethiopia

መተግበሪያ | X ላይ ይከተሉን

አዳዲስ ዜናዎች
0