የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቅቡልነት አሽቆልቁሎ 42 በመቶ ደረሷል ተባለ
20:19 17.04.2025 (የተሻሻለ: 20:34 17.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቅቡልነት አሽቆልቁሎ 42 በመቶ ደረሷል ተባለ
ዘ ኢኮኖሚስት እና ዩጎቭ ያካሄዱት የሕዝብ አስተያየት ጥናት 52 በመቶ ምላሽ ሰጪዎች ለትራምፕ የእስካሁን አፈጻጸም አሉታዊ አመለካከት እንዳላቸው አሳይቷል።
በተመሳሳይ በሕዝብ አስተያየቱ መሠረት በጥናቱ የተሳተፉ 35 በመቶ ሴቶች ትራምፕን ሲቃወሙ፤ 49 በመቶ የሚሆኑ ወንዶች ፕሬዝዳንቱን ይደግፋሉ።
ከሚያዚያ 5 እስከ 7 በተደረገው ጥናት 1 ሺህ 512 ሰዎች ተሳትፈዋል።
ዎል ስትሪት ጆርናል በቅርቡ አካሂዶት በነበረው የሕዝብ አስተያየት መስጫ የትራምፕ ቅቡልነት 46 በመቶ እንደነበር ገልጿል።
@sputnik_ethiopia