ትራምፕ እስራኤል በግንቦት ወር የኢራን የኒውክሌር ተቋማትን እንዳታጠቃ መከልከላቸውን አንድ ሪፖርት አመላከተ
14:08 17.04.2025 (የተሻሻለ: 14:24 17.04.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱትራምፕ እስራኤል በግንቦት ወር የኢራን የኒውክሌር ተቋማትን እንዳታጠቃ መከልከላቸውን አንድ ሪፖርት አመላከተ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ትራምፕ እስራኤል በግንቦት ወር የኢራን የኒውክሌር ተቋማትን እንዳታጠቃ መከልከላቸውን አንድ ሪፖርት አመላከተ
ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ዲፕሎማሲን መከተል ወይም እስራኤልን መከላከል በሚለው ጉዳይ ላይ ለወራት የውስጥ ድርድር ካደረጉ በኋላ ውሳኔው ላይ ደርሰዋል ሲል ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
በዘገባው መሠረት የእስራኤል ባለስልጣናት የቴህራን የኒውክሌር ፕሮግራምን ቢያንስ በአንድ ዓመት ወደ ኋላ ለመመለስ በማሰብ የኒውክሌር ተቋማቷን ለመምታት ተዘጋጅተው እንደነበር ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጿል።
የኢራን እና አሜሪካ የመጀመሪያ ዙር ድርድራቸውን ባለፈው ቅዳሜ አካሂደዋል። ሁለቱ ወገኖች ውይይቱ ገንቢ እና አዎንታዊ እንደነበር ገልጸዋል። ቀጣዩ ዙር ውይይት ቅዳሜ ይካሄዳል።
@sputnik_ethiopia