ትራምፕ እስራኤል በግንቦት ወር የኢራን የኒውክሌር ተቋማትን እንዳታጠቃ መከልከላቸውን አንድ ሪፖርት አመላከተ
14:08 17.04.2025 (የተሻሻለ: 14:24 17.04.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ትራምፕ እስራኤል በግንቦት ወር የኢራን የኒውክሌር ተቋማትን እንዳታጠቃ መከልከላቸውን አንድ ሪፖርት አመላከተ
ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ዲፕሎማሲን መከተል ወይም እስራኤልን መከላከል በሚለው ጉዳይ ላይ ለወራት የውስጥ ድርድር ካደረጉ በኋላ ውሳኔው ላይ ደርሰዋል ሲል ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
በዘገባው መሠረት የእስራኤል ባለስልጣናት የቴህራን የኒውክሌር ፕሮግራምን ቢያንስ በአንድ ዓመት ወደ ኋላ ለመመለስ በማሰብ የኒውክሌር ተቋማቷን ለመምታት ተዘጋጅተው እንደነበር ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጿል።
የኢራን እና አሜሪካ የመጀመሪያ ዙር ድርድራቸውን ባለፈው ቅዳሜ አካሂደዋል። ሁለቱ ወገኖች ውይይቱ ገንቢ እና አዎንታዊ እንደነበር ገልጸዋል። ቀጣዩ ዙር ውይይት ቅዳሜ ይካሄዳል።
@sputnik_ethiopia